Friday, 21 March 2014

INSA የማን ነው? የኢህአዴግ ወይስ የህዝብ?




ወደ ድረ ገጹ ስትገቡ ከፊት ለፊት የምታዩት የሚያስፈራ ሎጎ በሸረሪት ድር፣ በቁልፍና የቁልፍ ጋን ተደጋግፈው የሰሩት የተቋሙ መጠሪያ ሲታዩ እንደተቋሙ አላማ ደህንነትን ሳይሆን ስጋትን ይፈጥራሉ። (INSA) የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ። “Secured Cyber for Peace, Development and Democracy” የተቋሙ ሞቶ ነው።

የዚህ ተቋም ስልጣን አገሪቷን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ስነልቦናዊ ቀውስ ውስጥ ሊከቱ ይችላሉ ብለው የጠረጠሯቸው አካላት ላይ ካለ ፍርድ ቤት ፈቃድ ድንገተኛ ምርመራና ብርበራ ያካሂዳል። ይህ ተቋም አደጋ ያመጣሉ ብሎ ያሰበውን ማንኛውም እንደ ኢንተርኔት ግንኙነት፣ ኮምፒውተሮች፣ የተለያዩ ኔትውርኮች፣ የሬድዮና የተሌቪዝን ስርጭቶች እና ማህበራዊ ድረገጾች ፌስቡክን ጨምሮ አስፈላጊውን ክትትልና ምርመራ እንዲያደርግባቸው ከተቃዋሚ ፓርቲ አንድ ተወካይ ብቻ ያለው የኢትዮጵያ ፓርላማ ሙሉ ስልጣን ሰጥቶታል።

የስለላ መሳሪያዎችን በብዙ ሚሊዮን ዶላሮች እየገዛ የሚያስገባው የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን የኢንተርኔት ግንኙነት መሰለል ብቻ ሳይሆን በብዙ ሚሊዮን ዶላሮች እየተገዙ በሚመጡ መሳሪያዎች የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣብያዎችንና የሳተላይት ቴሌቭዝኖችን በማገድ ዜጎቻቸውን በስለላ ፋታ ከነሱት ኢራንና ቻይና ተርታ ተመድቧል።

“Secured Cyber for Peace, Development and Democracy”

ጋዜጠኖች፣ ተቃዋሚዎች እንዲሁም መንግስት ላይ ከፍተኛ ትችት የሚሰነዝሩ ግለሰቦች ያለጥርጥር በዚህ መስሪያ ቤት እይታ ውስጥ ናቸው። የተለያዩ ጥናቶችና ሪፖርቶች የሚያመለክቱትም የኢትዮጵያ መንግስት አሸባሪዎችን